ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ተክለሃይማኖት ሕፃናት በወረብ አገልግሎት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዋሽንግተን ዲሲና አካባቢዋ ሃገረ ስብከት የምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን የነገዋ የቤተክርስቲያን ተተኪ ሕፃናት በእለተ ሰንበት በወረብ አገልግሎት ላይ
ሕፃናቱን በጥበብ በሞገስ ያሳድግልን አሜን
በመስቀሉ ደም ሰላምን አደረገ

የመዝሙር ካሴት በገበያ ላይ

ኢትዮጵያዊው ብርሃን
ኢትዮጵያዊው ብርሃን አቡነ ተክለ ሃይማኖት በሰሜን ሸዋ ቡልጋ ጽላልሽ ወይም ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰበካ ክልል ከአባታቸው ከካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ቅድስት እግዚእ ኃረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው፤ በ፲፩፻፺፯ ዓ.ም ታሕሣሥ ፳፬ ቀን ተወለዱ፡፡
በተወለዱ በሦስት ቀናቸው ከእናታቸው እቅፍ ወርደው «አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» ብለው ሥላሴን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ትርጓሜውም የጽዮን ተድላዋ ወይም ደስታዋ ማለት ነው፡፡ አባታቸው የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሲያስተምሯቸው አካባበቢያቸው ደግሞ በዘመኑ የነበሩ ልጆች ይማሩ የነበረውን ፈረስ መጋለብን፣ ቀስት መወርወርን፣ እርሻን እና አደንን አስተምረዋቸዋል፡፡