ቅዳሴ እና መጽሐፍ ቅዱስ
በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ
ቤተ ክርስቲያናችን ሥጋ ወደሙን የምታከብርበት የተለየ ሥርዓተ ጸሎት አላት፡፡ ይህ ልዩ የምስጋና ጸሎት ‹‹ጸሎተ ቅዳሴ›› ይባላል፡፡ ያለ ጸሎተ ቅዳሴ ሥጋ ወደሙ አይዘጋጀም (አይፈተትም)፡፡ ያለ ሥጋ ወደሙም ቅዳሴ አይቀደስም፡፡
በቤተ ክርስቲያን የታወቁና እስከአሁንም በአገልግሎት ላይ ያሉ ቅዳሴያት በዓይነት 14 ሲሆኑ ቀደም ባሉት ዘመናት በተለይ በወርኀ ጽጌ ይቀደስ የነበረ ‹‹መዓዛ ቅዳሴ›› የሚባል 15ኛ ቅዳሴም በቤተ ክርስቲያናችን ይገኛል፡፡
ጸሎተ ቅዳሴ መሠረቱ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ የዚህ አጭር ገጸ ንባብ /የመግቢያ ንግግር/ ዓይነተኛ ዓላማ ቅዳሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው መሆኑን ግልጽ ማድረግ ነው፡፡
መልክዐ ተክለሃማኖት - ክፍል ሶስት
፪. ሰላም ለዝክረ ስምከ በጥንተ ፊደሉ መስቀል ስም ክቡር ወስምልዑል። ተክለሃማኖት ማቴዎስ በዓለ ቀዳማይ ወንጌል ከመእወድሰከ መጠነ አውሥኦተ እክል። ማዕሠረ ልሳንየ ትፍታሕማርያም ድንግል።
ትርጉም
የስምሀ መነሻፊደል የመስቀልምልክት ለሆነውእና ክቡር ገናናለሆነው ስምአጠራርህ ሰላምእላለው ።የወንጌልተቀዳሚ ስምማቴዎስየተባልክተክለሃይማኖትሆይ እንደችሎታዬአመሰግንህ ዘንድአንደበቴ ትፈታልኝ ዘንድ ድንግል ማርያምን እማልዳለሁ።
የአባታችን የቅዱስ ተክለሃማኖት የስማቸው መነሻ ፊደል ’ተ’ የመስቀል ቅርጽ ያለው ነው የስማቸውም ትርጉም ተክለ አብተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው። ይህም በስማቸው ላይ ስመ እግዚአብሔር እንዳለ ያስረዳናል። በገድላቸው እንደተጻፈው ይህንን ስም አባታችን ያገኙት የመንፈሳዊ ተጋድⶀአችው የቅርብ ረዳት በሆነው በቅዱስ ሚካኤል አማካኝነት ነው ገድ ተክ፳፰ ፤፲፪ የቀድሞ ስማቸው ፍስሐ ጽዮን ነው ትርጉሙም የጽዮን ፤የቤተክርስትያን ፤የእመቤታችን ደስታ ማለት ነው ። በአጠቃላይየአባታችን የቅዱስ ተክለሃይማኖት ስም የእግዚአብሄርን ክብር የሚገልጽ ልዩ መንፈሳዊ መልክዕት የያዘ ስም ነው። ስለስማቸው ለመግቢያ ያህል ይህንን ካልን መጽሐፍ ቅዱስ ስለቅዱሳን ስም ምንእንደሚል አንዳንድ ነገሮችን እንመልከት።
፩. በቅዱሳን ስም ላይ የእግዚአብሔር ስም ይከብራል
« በፊቱ ተጠንቀቁ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሰሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት» ዘጸ፳፫፤፳፩
መልክዐ ተክለ ሃይማኖት - ክፍል ሁለት
፩. ሰላም ለፅንሰትከ ወለልደት ከእምከርሥ። አመ ዕሥራ ውረቡዑ ለወርኃ ታኅሣሥ። ተክለሃይማኖት በኩሉ ወበውስተ ኰሉውዱስ። ናሁ ወጠንኩ ወዕቤ ለስብሓቲከ ሐዲስ። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ።"
ትርጉም
ተክለሃይማኖት ሆይ አስቀድሞ በማህጸን ለተጸነስከው ጽንሰትህና በታህሳስ ሃያ ዐራት ቀን ለተወለድከው መወለድህም ሰላም እላለው በሁሉ ዘንድ የተመሰገንክ ተክለሃይማኖት ሆይ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብዬ አዲስ የሚሆን ምስጋናህን እጀምራለሁ።
በክፍል አንድ ጽሑፋችን ሰላም ለፅንሰትከወለልደትከ እምከርሥ። አመ ዕሥራ ውረቡዑ ለወርኃ ታኅሣሥ። የሚለውን የአባታችንን ፅንሰታቸውን እና ልደታቸውን የሚያወድሰውን ክፍል ተመልክተን ነበር በዚህ ጽሁፋችን ደግሞ ተክለሃይማኖት በኩሉወበውስተ ኰሉውዱስ ። ናሁ ወጠንኩ ወዕቤ ለስብሓቲከ ሐዲስ። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ። ትርጉም ፤ በሁሉ ዘንድየተመሰገንክ ተክለሃይማኖት ሆይ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ ብዬ አዲስ የሚሆን ምስጋናህን እጀምራለሁ።
በቅድስት ቤተክርስትያን ስርአት መሰረት የማንኛውም ተግባር መጀመርያ ስመ ስላሴን መጥራት ነው የምታድርጉትን ሁሉበጌታ ስም አድርጉት ስለተባለ የጸሎትም መጀመርያ በስላሴ ስም ማማተብ ነው ምእምናን ጸጋ የሚያግኙበት የእግዚአብሔር ልጆች የሚሆኑበት ምስጢረ ጥምቀተት እንኳን የሚፈጸመው በአብ በወልድ እና በመንፈስ ቅዱስ ስም ነው ማቴ ፳፰፤፲፱ ለዚህም ነውየአባታችን ምልክዐ ጸሎታቸው ሲጀመር በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ የተባለው ። ይህም እያንዳንዱ ክርስትያን የግልምሆነ የማህበር ጸሎት ሲያደርግ በስላሴ ስም ማማተብ እንዲገባ ያስተምረናል ጌታም በወንጌል እንዲህ ብሎ ነግሮናል «ወደ አብ እሄዳለውና አብም ስለወልድ እንዲከበር በስሜየምትለምኑትን ሁሉ እኔ አደርገዋለሁ» ዮሐ ፲፬፡፲፫ በተጨማሪም «በዚያን ቀን በስሜ ትለምናላችሁ እኔም ስለናንተአብን እንድለምን የምላችሁ አይደለሁም»ዮሐ፲፮፡፪፮