ትምህርተ ሃይማኖት - ክፍል ፪
ትምህርተ ሃይማኖት - ክፍል ፩
የምስራቀ ፀሐይ ቅዱስ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሠንበት ትምህርት ቤት አመሰራረት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የምስራቀ ፀሐይ ቅዱስ ተክለሃይማኖት ሠንበት ትምሕህርት ቤ/ት በእግዚአብሄር ፈቃድና በብፁዕ አቡነ አብርሃም ሠብሳቢነት በጥቂት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ተመስርቷል ። ለዚህ አጥቢያ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያዎቹ የሠንበት ትምህርት ቤቱ አባላት በተለይ በተለያዩ በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ካሉ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ሠንበት ትምህርት ቤት መጥትው የተሰባሰቡ በመሆናቸው በፊትም በሠንበት ትምህርት ቤት አገልግሎት የሚታወቁ ስለነበረ ለመሰባሰብና ለመነጋገር ስለ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ቀናዒ ስለነበሩ እና ለመስራትና በተለይም በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ዓርአያ የሚሆን በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የሚጓዝ ሠንበት ትምህርት ቤት ለመመስረት ብዙ ውጣ ውረድ ነበረበት።
ለሠንበት ትምህርት ቤቱ አገልግሎትና አባላቱን ለማሰባሰብ ትልቅ ፈተና የነበረው የትምህርት መማርያና የሠንበት ትምህርት ቤትን ጉባኤና መርሃ ግብሩን ማከናወኛ ቦታ ያለመኖር ነበር ። በወቅቱ በብፁዕ አቡነ አብርሃም ጠቋሚነት የሠንበት ትምህርት ቤቱን በቋሚነት ለማቋቋም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ሲፋጠኑ በሚያዩዋቸው አገልጋዮች አማካኝነት የሠንበት ትምህርት ቤቱ የመጀመርያው ሥራ አመራር ሰባት አባላት ያሉት ኮሚቴ ተዋቀረ ። በወቅቱ የተመረጡት ሥራ አመራሮች ትልቁ ጭንቀትና የዘወትር ውይይታቸው የነበረው እንዴት ዓርአያ የሚሆኑ ወጣቶች በሠንበት ትምህርት ቤት እናዋቅርና እንቅረፅ ፣ አባላትስ እንዴት እናሰባስብ ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱም በኪራይ ስለነበረች ትምህርት እንዴት እና የት ይሰጥ ፣ መዝሙርስ የት ይጠና ፣ ለሠንበት ትምህርት ቤቱስ አገልግሎት የሚውሉ አልባሳትና ቁሳቁሶች እንዴት እናግኝና እናሟላ ነበር ። በወቅቱ በቦታ ማጣት ምክንያት ለእሁድ አገልግሎት የሚሆን መዝሙር የሚጠናው በወቅቱ ቤተ ክርስቲያኒቱ ተከራይታ ትጠቀምበት የነበረው የሌላ እምነት ተከታዮች ስለነበረ እነሱ ለአገልግሎት ይጠቀሙበት በነበረ “ፒያኖ“ ዙሪያ ፒያኖውን እንደ ጠረጴዛ በመጠቀም መዝሙር ያጠኑ ነበረ ። እንደውም ከመስራቾቹ አንድ ወንድም ወደፊት ይቺን ፒያኖ በትዝታ የምናስብበት ጊዜ ይመጣል ብሎ አባላቱን ፈገግ አሰኝቷል ።